ኢሳ አልመሲህንና መስቀልን በህልም ማየትና ትርጉሞቻቸው

አል-መሲህን (ሠላሙ በእኛ ላይ ይሁን) በእሻራ (በህልም) ማየት ከስጋት፣ ከህመም፣ እና ከበሽታ ነጻ የመውጣት መልካም ዜና ነው፡፡

አንድ ሰው የኢሳ አል-መሲህን (ሠላሙ በእኛ ላይ ይሁን) መወለድ በህልሙ ካየ፤ በአላህ ፈቃድ፤ መልካም ዜናን ወይም የሚያስደስት ክስተትን ይሰብካል ማለት ነው፡፡ ክርስቶስን (ሠላሙ በእኛ ላይ ይሁን) ከነአሥራ ሁለቱ ደረሳዎቹ የሚያይ ከሆነ በመልካም ወዳጅነት ወይም ህብረት የተባረከ ነው ማለት ነው፡፡ እንደዚሁም ደቀመዝሙሩ (ደረሳው) ለመሆንና እነርሱ የኖሩትን ህይወት እንድትኖር የቀረበልህ ጥሪ ነው ማለት ነው፡፡ ስለዚህ የኢሳ አል-መሲህ (ሠላሙ በእኛ ላይ ይሁን) በህልም መገለጥ ደህንነትን፣ እርጋታንና ዘላቂ ሰላምን የማግኘት ትንቢት ነው፡፡

አንድ ሰው ኢሳ አል-መሲህ (ሠላሙ በእኛ ላይ ይሁን) በህልሙ ጭንቅላቱን ሲዳብስለት ወይም አካሉን በዘይት ወይም በውሃ ሲያብስለት ቢያይ ሰውዬው በሽተኛ ከሆነ ይፈወሳል፤ እሰረኛ ከሆነ ይፈታል፡፡ አንዲት ሴት እርጉዝ ሆና ኢሳ አል-መሲህ (ሠላሙ በእኛ ላይ ይሁን) በህልሟ ጭንቅላቷን በእጆቹ ሲዳብስ ብታይ በቀላሉ፤ ያለድካም፣ ያለህመም፣ ያለመከራ ልጇን እንደምትገላገልና ልጇንም ለእርሱ እንድትቀድስለት የቀረበላት ጥሪ መሆኑን ያሳያል፡፡

ማንም ሰው ኢሳ አል-መሲህ (ሠላሙ በእኛ ላይ ይሁን) ዳግም ሲመለስ ወይም ከሞት ሲነሳ በህልሙ ቢያየው ያ ሰው በሌላ ሃገር የሚኖር ከሆነ ወይም ተጓዥ ከሆነ ወደ ቤተሰቡና ወደ ሃገሩ እንደሚመለስ ያሳያል፡፡ ኢሳ አል-መሲህ (ሠላሙ በእኛ ላይ ይሁን) ሞትን ድል እንዳደረገ፣ እንደዚሁም ወደ ሰማያዊ ጀነት እንደሚወስደን የገባልንን ቃል የሚያስረግጥ በጣም ወሳኝ ማረጋገጫ ነው፡፡

አንድ ሰው የሆነ ነገርን በልቡ ተመኝቶ ኢሳ አል-መሲህን (ሠላሙ በእኛ ላይ ይሁን) በህልሙ ከፊት ለፊቱ ሲቀመጥ፣ ከእርሱ ጋር ሲቀመጥ፣ ከእርሱ ጋር ሲነጋገር ቢያይ ያ ምኞቱ እንደሚፈጻም የሚያሳይ ሲሆን እንደዚሁም የእውነተኛ ፍቅር መግለጫም ነው፡፡

ማንም ሰው ኢሳ አል-መሲህን (ሠላሙ በእኛ ላይ ይሁን) በእሻራ ቢያይ ይህ የቅንነቱና ለጋስነቱ ምልክት ነው፡፡ ኢሳ (ሠላሙ በእኛ ላይ ይሁን) የሆነ ቃል ቢናገረው እውነትን ይናገራል፤ ምክንያቱም ኢሳ (ሠላሙ በእኛ ላይ ይሁን) የአላህ ቃል ነው፡፡

ማንም ሰው ኢሳ አል-መሲህ (ሠላሙ በእኛ ላይ ይሁን) በህልሙ ወደ ቤቱ ሲገባ ቢያይ ያ ሰው በዚህ ስፍራ በደህንነት፣ በእርጋታና በበረከት ይኖራል ማለት ነው፡፡ እንደዚሁም ኢሳ አል-መሲህ (ሠላሙ በእኛ ላይ ይሁን) ከእንጀራው ሲቆርስ በህልሙ ቢያይ ያ ሰው ለህይወቱ ሁሉ የሚበቃው በቂ ነገር ይኖረዋል ማለት ነው፡፡ በተጨማሪም አንድ ሰው ኢሳ (ሠላሙ በእኛ ላይ ይሁን) ከእርሱ ጋር በማዕድ ሲበላ ቢያይ ድህነትን አያይም ወይም ምንም ነገር አይጎድልበትም ይባላል፡፡

እንደዚሁም ኢሳ አል-መሲህን (ሠላሙ በእኛ ላይ ይሁን) በህልም ማየት የሚፈፀም ቃልኪዳንን ያመላክታል፡፡ ማንም እርሱን በመስቀል ላይ ቢያየው ከስቃይ እንደሚያመልጥና ንፁህ የሆነውን ፍቅሩን እንደሚቀበልና ከሞትና ከሃጢያት እንደሚድን ያሳያል፡፡

በህልም መስቀልን ማየት በአጠቃላይ የርህራሄን ባህሪይ ያመላክታል፡፡ አደጋን፣ ክፋትን፣ ወይም ፍትወትን ማሸነፍን ያመላክታል፡፡ ምክንያቱም የህይወትህን ምኞት፣ ፍትወትና ክፋትን እየሰቀልክ እንደሆነ ስለሚያሳይ ነው፡፡ በህልምህ መስቀልን በደረትህ ላይ አንጠልጥለህ ብታይ ቅንነትህን፣ መሰጠትህንና ለሌሎች (ለወዳጆችህ፣ ለጓደኞችህና የቅርብ ሰዎችህ ለሆኑት) መስዋዕት ለመሆን ፈቃደኛ መሆንህን ያመላክታል፡፡

መስቀልን በእሻራ ማየት በጸጋና በእውነት የተሞላ የአዲስ ህይወት ጅማሮን የሚያበስር ነው፡፡ አንድ ሰው በህልም መስቀል ያለው የአንገት ሀብል ሲያበረክትልሽ ብታይ የችግርሽ መቋጫና የህይወትሽ መሰናክሎች ማብቂያ መድረሱን ያመላክታል፡፡ ራሱ ሲሰቀል ወይም በመስቀል ላይ ሲሰቃይ በህልም የሚያይ ሰው በህይወቱ/ቷ መስዋዕትነትን የሚጠይቅ ነገር እንደሚገጥመው/ማት ወይም በማህበረሰብ ውስጥ ትልቅ ሚና እንደሚጫወት፣ እና በህይወቱ የተሃድሶ አራማጆችን ጎዳና እንደሚከተል ያመላክታል፡፡

ኢ-ፖስታ አድራሻወ ይፋ አይደረግም። መሞላት ያለባቸው መስኮች * ምልክት አላቸው

  1. السلام عليكم. حلمت اني رجعت إلى بيتي في بلدي بعد ان كان بها حرب وكان في ناس كثير راجعة إلى بيوتها ولكن شكل المنطقة كان مختلف وفي بيتنا كان هناك كتاب الانجيل في وسط طاولة غرفة الجلوس.

    1. وعليكم السلام يا غادة. نشكرك لمشاركتنا حلمك الذي يحمل رسائل عميقة من الله. إن عودتك إلى بيتك في بلدك بعد الحرب، ورؤيتك للناس الكثيرين وهم يعودون إلى بيوتهم، ترمز إلى أن الله سبحانه وتعالى يعد قلبك لفترة جديدة من السلام والراحة والاستقرار الروحي بعد أيام مليئة بالاضطراب والقلق، فهو الإله الذي يجمع المشتتين ويرد النفوس إلى موضع الأمان معه، كما قال في الانجيل: “تَعَالَوْا إِلَيَّ يَا جَمِيعَ الْمُتْعَبِينَ وَالثَّقِيلِي الأَحْمَالِ، وَأَنَا أُرِيحُكُمْ” (الإنجيل، متى 11: 28). أما اختلاف شكل المنطقة فهو دلالة على أن الله يعمل بروحه لتجديد حياتك وتغيير ما مضى إلى الأفضل، إذ يقول: “هَا أَنَا أَصْنَعُ كُلَّ شَيْءٍ جَدِيدًا” (الإنجيل، رؤيا 21: 5). وأما رؤيتك لكتاب الانجيل في وسط طاولة غرفة الجلوس، فهي رسالة عظيمة ودعوة محبة من الله لك، بأن تضع كلمته المقدسة في وسط حياتك وبيتك وقلبك، لأن في الانجيل تجد الحق والنور والطريق إلى السلام الحقيقي الذي وعد به سيدنا عيسى المسيح (سلامه علينا) حين قال: “سَلاَمًا أَتْرُكُ لَكُمْ. سَلاَمِي أُعْطِيكُمْ. لَيْسَ كَمَا يُعْطِي الْعَالَمُ أُعْطِيكُمْ أَنَا. لاَ تَضْطَرِبْ قُلُوبُكُمْ وَلاَ تَرْهَبْ” (الإنجيل، يوحنا 14: 27). إن الله يدعوك من خلال هذا الحلم لأن تقترب منه بقراءة الانجيل والتأمل في كلماته، لتتعرف على شخص سيدنا عيسى المسيح الذي هو مصدر السلام الحقيقي الذي يفوق كل عقل. ننصحك بالبدء بقراءة الانجيل، ولا تتردد بالتواصل معنا لأي سؤال أو استفسار. بارك الله بك وحفظك ومنحك سلامه الدائم.

More Stories
يوم السبت فى القرآن